Telegram Group & Telegram Channel
“+" ሰሙነ ሕማማት ”+"

“ነሥአ ደዌነ መጾረ ሕማመነ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፣ ሕማማችንን ተሸከመ፣ ስለመተላለፋችን ቆሰለ፣ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን” (ኢሳ. 53÷4-6) በማለት ነቢዩ ኢሳይያስ የተነበየው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ከፍዳና ከዘለዓለማዊ ሞት ለማዳንና ከዲያብሎስም ቁራኝነት ነፃ ለመውጣት
ሲል 13ቱን ሕማማተ መስቀልና ሌሎቹንም ጸዋትወ መከራዎች የተቀበለበት ሳምንት “ሰሙነ ሕማማት” በመባል ይታወቃል፡፡ ትርጓሜውም የመከራ ሳምንት ማለት ነው፡፡ ከፋሲካ በፊት በጸሎትና በጾም፣ በብዙ ስግደት የክርስቶስ አዳኝነትና ቤዛነት የሚታሰብበት ይህ ሳምንት በልዩ ልዩ አብያተ ክርስቲያናት በተለያዩ ስሞች የሚጠራ ሲሆን እንደኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አጠራር ግን “ሕማማት” በሚል ስያሜ ይጠራል፡፡ እስከ 4ኛው ምእተ ዓመት ድረስ ጌታችን ከጾመው 40 ጾም ጋር ሳይሆን ለብቻው ይታሰብ እንደነበረ ከቤተ ክርስቲያን ታሪክ መረዳት ይቻላል፡፡ ምክንያቱም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእሱ ላይ የደረሱትን ጸሞትወ መከራዎች ሁሉ በትዕግሥት ተቀብሎና በመስቀል
ላይ ተሰቅሎ የሞተው 40ውን ጾም ከፈጸመ በኋላ ወዲያውኑ ሳይሆን ከሦስት ዓመታት በላይ ከአስተማረና ቤተ ክርስቲያንን ካደራጀ በኋላ
ስለሆነ ነው፡፡
በ4ኛው ምእት ዓመት ግን በምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክርስቶስ ከጾመው 40 ጾም ቀጥሎ ከትንሣኤ በፊት ባለው ሳምንት “ሰሙነ ሕማማት” እንዲታሰብ ተደርጓል፡፡ በዚህም ምክንያት የጾሙ ጊዜ ከ6 ወደ 7 ሳምንታት ከፍ ብሎአል፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ግን ከ40 ጾም በፊት ባለው መጀመሪያ ሳምንት ጾመ
ሕርቃል ተጨምሮ እንዲጾምና ከ40ው ጾም በኋላም “ሰሙነ ሕማማት” በጾም፣ በጸሎትና በስግደት እንዲታሰብ በመደረጉ የጾሙ ጊዜ 55 ቀናት ወይም 8 ሳምንታት ስለሆነ የነዚህ ድምር ውጤት ጾሙን ዐቢይ ጾም ሊያሰኘው ችሏል፡፡ ዐቢይ ጾም ማለትም ታላቁ ጾም ማለት ነው፡፡ የዚህ
የሰሙነ ሕማማት መታሰቢያ ጾም መጨረሻው የዓቢይ ጾምም መጨረሻ ስለሆነ ጾሙ በአክፍሎት ይደመደምና ከእሁድ መንፈቀ ሌሊት ጀምሮ
በዓለ ትንሣኤው ይከበራል፡፡ የምዕራብ ቤተክርስቲያን ደግሞ በኒቆዲሞስ የሰሙነ ሕማማትን መታሰቢያ ታደርግና በሆሳዕና ዕለት
የትንሣኤን በዓል ታከብራለች፡፡
በሰሙነ ሕማማት መጀመሪያ በሆሣዕና ዕለት የሚፈጸሙት አስደሳች ሥርዓቶች በኋላ በ6ኛው ምእት ዓመት እንደተጀመሩ ከቤተክርስቲያን
ታሪክ መረዳት ይቻላል፡፡
ለምሳሌ ያህል የዘንባባ ዝንጣፊ ባርኮ ለምእመናን ማደል፣ የዘንባባውን ዝንጣፊ በእጅ ይዞ መዘመርና በቤተክርስቲያን ዙሪያ ዑደት ማድረግ፣
በቤተክርስቲያኑ በሮችና ማዕዘኖች የዳዊት መዝሙራትን እየዘመሩ ወንጌልን ማንበብ፣ ሌሎችንም በዓሉን የሚመለከቱ ሥርዓተ
ቤተክርስቲያን መፈጸም የተጀመረው በዚሁ በ6ኛው ምእት ዓመት ሲሆን ይህም አስደሳች ሥርዓት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እስከዛሬ ድረስ እየተፈጸመ ይገኛል፤ ወደፊትም ይቀጥላል፡፡ ዘንባባ የክብርና የድል ምልክት ከመሆኑም በላይ ድርጊቱና አፈጻጸሙ ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በድል አድራጊነት ወደ ኢየሩሳሌም በገባበት ጊዜ የተደረገለትን የክብር አቀባበል የሚያመለክት ነው፡፡
በጸሎተ ሐሙስ ዕለትም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታና መምህር ሲሆን በትኅትና ራሱን ዝቅ አድርጎ የደቀ መዛሙርቱን እግር ያጠበ መሆኑን
ለማስታወስና ምሳሌውን ለመከተል ሲባል በፓትርያርክ፤ በሊቃነ ጳጳሳትና በሊቃነ ካህናት የካህናትንና የምእመናንን እግር የማጠብ
ሥርዓትም በዚሁ በ6ኛው ምእት ዓመት ተጀምሮአል፡፡
በሰሙነ ሕማማት የተፈጸሙ ታላላቅ ድርጊቶች:-
እሁድ የሆሣዕና ዕለት፡ – ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በድል አድራጊነት ወደ ኢየሩሳሌም በገባ ጊዜ ሕፃናትና ሽማግሌዎች፣
በጠቅላላ ሕዝቡ ሁሉ ልብሳቸውን እያነጠፉና ቅጠል እየጎዘገዙ፣ በእጃቸውም የድል አድራጊነት ምልክት የሆነውን የዘንባባ ዝንጣፊ እያያዙ በዝማሬና በታላቅ ክብር ተቀብለውታል፡፡

ሰኞ፡-በቤተ መቅደሱ ውስጥና በዙሪያው ይሸጡና ይገዙ የነበሩትን ከቤተ መቅደስ ያስወጣቸው፤ የገንዘብ ለመዋጮች ገበታዎችንና የርግብ
ሽያጮችን ወንበሮች ገልብጦ ሁሉንም ከቤተ መቅደሱ በጅራፍ ያባረራቸው፣ ፍሬ አልባ የሆንችውን በለስ የረገማት በዚሁ ዕለታተ ሰኑይ
ነው፡፡ በበለስም አንፃር ኃጢአትን እንደረገመ ሊቃውንት ያትታሉ፡፡

ማክሰኞ፡-ሰኞ የረገማት በለስ ማክሰኞ ደርቃ ተገኝታለች፡፡ የበለሲቱ መረገምና መድረቅ ቀድሞ በአዳም በኩል የመጣውና ከትውልድ ወደ
ትውልድ ሲተላለፍ የኖረው ኃጢአትና መርገም በክርስቶስ ሞት መወገዱን ያመለክታል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚሁ በማክሰኞ ቀን ስለግብር አከፋፈል፣ ስለትንሣኤ ሙታንና የዳዊት ልጅ የሚባል ማን እንደሆነ በመግለጥ መጻሕፍትን እየጠቀሰ ከፈሪሳውያን ጋር ይከራከር የነበረው በዚሁ ማክሰኞ በሚባለው ዕለተ ሠሉስ ነው፡፡ እንዲያውም ጸሐፍትና ፈሪሳውያንን በታላቅ ተግሣጽ ገሥጾአቸዋል (ማቴ. 23÷1-39)፣ በለምፃሙ፣ በስምዖን ቤት ማርያም እንተ እፍረት
ሽቶ የቀባችው፤ የአስቆርቱ ይሁዳ ጌታውን ለማስያዝ ከአይሁድ ጋር በድብቅ የተነጋገረው በዚሁ በዕለተ ማክሰኞ ነው፡፡

ረቡዕ፡-አይሁድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያዝና እንዲገደል ለማድረግ ውሳኔ የወሰኑበት እና ምክር የፈጸሙበት ቀን ነው፡፡ እንዴት እንደሚይዙት ማን እንደሚያስይዛቸውና መቼ እንደሚይዙት በዚሁ ዕለት ወስነዋል፡፡ ለክፉ ሥራቸው ተባባሪ ያደረጉትም ከአሥራ ሁለቱ ደቀ
መዛሙርት መካከል የጥፋት ልጅ የሆነውን የአስቆርቱ ይሁዳን ነበር ስለዚህ ዕለተ ረቡዕ ምክር የተፈጸመበትና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ተይዞ እንዲገደል ውሳኔ የተላለፈበት ቀን በመሆኑና ውሳኔውም ተግባራዊ ሆኖ ጌታችን የተሰቀለውና የሞተው በዕለተ ዓርብ በመሆኑ
የክርስቶስን መከራና የሰውን ልጅ ድኅነት ለማስታወስ ሲባል ከትንሣኤው በኋላ በአሉት 50 ቀናት ካልሆነ በቀር በየሳምንቱ ረቡዕና
ዓርብ ጾመ ድኅነት በሚል ስያሜ እንዲጾም ተደርጎአል፡፡

ሐሙስ፡-በዚህ ዕለት ጧት የፋሲካን በዓልና ዝግጅት እንዲያዘጋጁ ደቀ
መዛሙርቱን ወደ ከተማ የላከ ሲሆን ሐሙስ ማታ ለመጨረሻ ጊዜ የፋሲካን በዓል ከደቀ መዛሙርቱ ጋር አክብሮአል፡፡ በዚሁ ዕለት የኦሪቱን
ሥርዓት ለውጦ አዲስ ሥርዓተ ቁርባን ሠርቶአል (ማቴ. 26÷26-27)፡፡ በጌቴ ሴማኒ እየጸለየ ጸሎት ከችግርና ከፈተና እንደሚያድንም ለማስረዳት “ወደፈተና እንዳትገቡ ጸልዩ” በማለት ለደቀ መዛሙርቱ መመሪያና ትምህርት ሰጠ (ማቴ. 26÷40)፡፡ ይሁዳም የአይሁድን ጭፍሮች እየመራ ወደ ጌታውና መምህሩ በመቅረብ “ሰላም ለአንተ
ይሁን ብሎ ጫማውን በመሳም ለጭፍሮቹ አሳልፎ የሰጠው በዚሁ በዕለተ ሐሙስ ማታ ነው፡፡ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠብ” እኔ ጌታና
መምህር ስሆን እግራችሁን ከአጠብኩ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል፤ እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ
እናንተ ደግሞ እንዲሁ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁ” (ዮሐ. 13÷13-15) በማለት ትኅትናን በተግባር እየተረጎመና በድርጊት እያሳየ
ለቀደ መዛሙርቱ ያስተማረው በዚሁ ዕለት ነው፡፡ ይህ ቀን ጌታችን በመከራው ጊዜ በተዋሐደው ሥጋ ተገብቶ ወደ ባሕርይ አባቱ የጸለየበትና ስለጸሎትም ያስተማረበት በመሆኑ ዕለቱ ጸሎተ ሐሙስ በመባል ይታወቃል፡፡

ዐርብ፡-ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአይሁድ ተላልፎ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ ሌሊቱን በሙሉ ከአንዱ ገዥ ወደ ሌ



tg-me.com/rituaH/1538
Create:
Last Update:

“+" ሰሙነ ሕማማት ”+"

“ነሥአ ደዌነ መጾረ ሕማመነ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፣ ሕማማችንን ተሸከመ፣ ስለመተላለፋችን ቆሰለ፣ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን” (ኢሳ. 53÷4-6) በማለት ነቢዩ ኢሳይያስ የተነበየው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ከፍዳና ከዘለዓለማዊ ሞት ለማዳንና ከዲያብሎስም ቁራኝነት ነፃ ለመውጣት
ሲል 13ቱን ሕማማተ መስቀልና ሌሎቹንም ጸዋትወ መከራዎች የተቀበለበት ሳምንት “ሰሙነ ሕማማት” በመባል ይታወቃል፡፡ ትርጓሜውም የመከራ ሳምንት ማለት ነው፡፡ ከፋሲካ በፊት በጸሎትና በጾም፣ በብዙ ስግደት የክርስቶስ አዳኝነትና ቤዛነት የሚታሰብበት ይህ ሳምንት በልዩ ልዩ አብያተ ክርስቲያናት በተለያዩ ስሞች የሚጠራ ሲሆን እንደኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አጠራር ግን “ሕማማት” በሚል ስያሜ ይጠራል፡፡ እስከ 4ኛው ምእተ ዓመት ድረስ ጌታችን ከጾመው 40 ጾም ጋር ሳይሆን ለብቻው ይታሰብ እንደነበረ ከቤተ ክርስቲያን ታሪክ መረዳት ይቻላል፡፡ ምክንያቱም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእሱ ላይ የደረሱትን ጸሞትወ መከራዎች ሁሉ በትዕግሥት ተቀብሎና በመስቀል
ላይ ተሰቅሎ የሞተው 40ውን ጾም ከፈጸመ በኋላ ወዲያውኑ ሳይሆን ከሦስት ዓመታት በላይ ከአስተማረና ቤተ ክርስቲያንን ካደራጀ በኋላ
ስለሆነ ነው፡፡
በ4ኛው ምእት ዓመት ግን በምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክርስቶስ ከጾመው 40 ጾም ቀጥሎ ከትንሣኤ በፊት ባለው ሳምንት “ሰሙነ ሕማማት” እንዲታሰብ ተደርጓል፡፡ በዚህም ምክንያት የጾሙ ጊዜ ከ6 ወደ 7 ሳምንታት ከፍ ብሎአል፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ግን ከ40 ጾም በፊት ባለው መጀመሪያ ሳምንት ጾመ
ሕርቃል ተጨምሮ እንዲጾምና ከ40ው ጾም በኋላም “ሰሙነ ሕማማት” በጾም፣ በጸሎትና በስግደት እንዲታሰብ በመደረጉ የጾሙ ጊዜ 55 ቀናት ወይም 8 ሳምንታት ስለሆነ የነዚህ ድምር ውጤት ጾሙን ዐቢይ ጾም ሊያሰኘው ችሏል፡፡ ዐቢይ ጾም ማለትም ታላቁ ጾም ማለት ነው፡፡ የዚህ
የሰሙነ ሕማማት መታሰቢያ ጾም መጨረሻው የዓቢይ ጾምም መጨረሻ ስለሆነ ጾሙ በአክፍሎት ይደመደምና ከእሁድ መንፈቀ ሌሊት ጀምሮ
በዓለ ትንሣኤው ይከበራል፡፡ የምዕራብ ቤተክርስቲያን ደግሞ በኒቆዲሞስ የሰሙነ ሕማማትን መታሰቢያ ታደርግና በሆሳዕና ዕለት
የትንሣኤን በዓል ታከብራለች፡፡
በሰሙነ ሕማማት መጀመሪያ በሆሣዕና ዕለት የሚፈጸሙት አስደሳች ሥርዓቶች በኋላ በ6ኛው ምእት ዓመት እንደተጀመሩ ከቤተክርስቲያን
ታሪክ መረዳት ይቻላል፡፡
ለምሳሌ ያህል የዘንባባ ዝንጣፊ ባርኮ ለምእመናን ማደል፣ የዘንባባውን ዝንጣፊ በእጅ ይዞ መዘመርና በቤተክርስቲያን ዙሪያ ዑደት ማድረግ፣
በቤተክርስቲያኑ በሮችና ማዕዘኖች የዳዊት መዝሙራትን እየዘመሩ ወንጌልን ማንበብ፣ ሌሎችንም በዓሉን የሚመለከቱ ሥርዓተ
ቤተክርስቲያን መፈጸም የተጀመረው በዚሁ በ6ኛው ምእት ዓመት ሲሆን ይህም አስደሳች ሥርዓት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እስከዛሬ ድረስ እየተፈጸመ ይገኛል፤ ወደፊትም ይቀጥላል፡፡ ዘንባባ የክብርና የድል ምልክት ከመሆኑም በላይ ድርጊቱና አፈጻጸሙ ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በድል አድራጊነት ወደ ኢየሩሳሌም በገባበት ጊዜ የተደረገለትን የክብር አቀባበል የሚያመለክት ነው፡፡
በጸሎተ ሐሙስ ዕለትም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታና መምህር ሲሆን በትኅትና ራሱን ዝቅ አድርጎ የደቀ መዛሙርቱን እግር ያጠበ መሆኑን
ለማስታወስና ምሳሌውን ለመከተል ሲባል በፓትርያርክ፤ በሊቃነ ጳጳሳትና በሊቃነ ካህናት የካህናትንና የምእመናንን እግር የማጠብ
ሥርዓትም በዚሁ በ6ኛው ምእት ዓመት ተጀምሮአል፡፡
በሰሙነ ሕማማት የተፈጸሙ ታላላቅ ድርጊቶች:-
እሁድ የሆሣዕና ዕለት፡ – ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በድል አድራጊነት ወደ ኢየሩሳሌም በገባ ጊዜ ሕፃናትና ሽማግሌዎች፣
በጠቅላላ ሕዝቡ ሁሉ ልብሳቸውን እያነጠፉና ቅጠል እየጎዘገዙ፣ በእጃቸውም የድል አድራጊነት ምልክት የሆነውን የዘንባባ ዝንጣፊ እያያዙ በዝማሬና በታላቅ ክብር ተቀብለውታል፡፡

ሰኞ፡-በቤተ መቅደሱ ውስጥና በዙሪያው ይሸጡና ይገዙ የነበሩትን ከቤተ መቅደስ ያስወጣቸው፤ የገንዘብ ለመዋጮች ገበታዎችንና የርግብ
ሽያጮችን ወንበሮች ገልብጦ ሁሉንም ከቤተ መቅደሱ በጅራፍ ያባረራቸው፣ ፍሬ አልባ የሆንችውን በለስ የረገማት በዚሁ ዕለታተ ሰኑይ
ነው፡፡ በበለስም አንፃር ኃጢአትን እንደረገመ ሊቃውንት ያትታሉ፡፡

ማክሰኞ፡-ሰኞ የረገማት በለስ ማክሰኞ ደርቃ ተገኝታለች፡፡ የበለሲቱ መረገምና መድረቅ ቀድሞ በአዳም በኩል የመጣውና ከትውልድ ወደ
ትውልድ ሲተላለፍ የኖረው ኃጢአትና መርገም በክርስቶስ ሞት መወገዱን ያመለክታል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚሁ በማክሰኞ ቀን ስለግብር አከፋፈል፣ ስለትንሣኤ ሙታንና የዳዊት ልጅ የሚባል ማን እንደሆነ በመግለጥ መጻሕፍትን እየጠቀሰ ከፈሪሳውያን ጋር ይከራከር የነበረው በዚሁ ማክሰኞ በሚባለው ዕለተ ሠሉስ ነው፡፡ እንዲያውም ጸሐፍትና ፈሪሳውያንን በታላቅ ተግሣጽ ገሥጾአቸዋል (ማቴ. 23÷1-39)፣ በለምፃሙ፣ በስምዖን ቤት ማርያም እንተ እፍረት
ሽቶ የቀባችው፤ የአስቆርቱ ይሁዳ ጌታውን ለማስያዝ ከአይሁድ ጋር በድብቅ የተነጋገረው በዚሁ በዕለተ ማክሰኞ ነው፡፡

ረቡዕ፡-አይሁድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያዝና እንዲገደል ለማድረግ ውሳኔ የወሰኑበት እና ምክር የፈጸሙበት ቀን ነው፡፡ እንዴት እንደሚይዙት ማን እንደሚያስይዛቸውና መቼ እንደሚይዙት በዚሁ ዕለት ወስነዋል፡፡ ለክፉ ሥራቸው ተባባሪ ያደረጉትም ከአሥራ ሁለቱ ደቀ
መዛሙርት መካከል የጥፋት ልጅ የሆነውን የአስቆርቱ ይሁዳን ነበር ስለዚህ ዕለተ ረቡዕ ምክር የተፈጸመበትና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ተይዞ እንዲገደል ውሳኔ የተላለፈበት ቀን በመሆኑና ውሳኔውም ተግባራዊ ሆኖ ጌታችን የተሰቀለውና የሞተው በዕለተ ዓርብ በመሆኑ
የክርስቶስን መከራና የሰውን ልጅ ድኅነት ለማስታወስ ሲባል ከትንሣኤው በኋላ በአሉት 50 ቀናት ካልሆነ በቀር በየሳምንቱ ረቡዕና
ዓርብ ጾመ ድኅነት በሚል ስያሜ እንዲጾም ተደርጎአል፡፡

ሐሙስ፡-በዚህ ዕለት ጧት የፋሲካን በዓልና ዝግጅት እንዲያዘጋጁ ደቀ
መዛሙርቱን ወደ ከተማ የላከ ሲሆን ሐሙስ ማታ ለመጨረሻ ጊዜ የፋሲካን በዓል ከደቀ መዛሙርቱ ጋር አክብሮአል፡፡ በዚሁ ዕለት የኦሪቱን
ሥርዓት ለውጦ አዲስ ሥርዓተ ቁርባን ሠርቶአል (ማቴ. 26÷26-27)፡፡ በጌቴ ሴማኒ እየጸለየ ጸሎት ከችግርና ከፈተና እንደሚያድንም ለማስረዳት “ወደፈተና እንዳትገቡ ጸልዩ” በማለት ለደቀ መዛሙርቱ መመሪያና ትምህርት ሰጠ (ማቴ. 26÷40)፡፡ ይሁዳም የአይሁድን ጭፍሮች እየመራ ወደ ጌታውና መምህሩ በመቅረብ “ሰላም ለአንተ
ይሁን ብሎ ጫማውን በመሳም ለጭፍሮቹ አሳልፎ የሰጠው በዚሁ በዕለተ ሐሙስ ማታ ነው፡፡ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠብ” እኔ ጌታና
መምህር ስሆን እግራችሁን ከአጠብኩ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል፤ እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ
እናንተ ደግሞ እንዲሁ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁ” (ዮሐ. 13÷13-15) በማለት ትኅትናን በተግባር እየተረጎመና በድርጊት እያሳየ
ለቀደ መዛሙርቱ ያስተማረው በዚሁ ዕለት ነው፡፡ ይህ ቀን ጌታችን በመከራው ጊዜ በተዋሐደው ሥጋ ተገብቶ ወደ ባሕርይ አባቱ የጸለየበትና ስለጸሎትም ያስተማረበት በመሆኑ ዕለቱ ጸሎተ ሐሙስ በመባል ይታወቃል፡፡

ዐርብ፡-ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአይሁድ ተላልፎ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ ሌሊቱን በሙሉ ከአንዱ ገዥ ወደ ሌ

BY ርቱዓ ሃይማኖት


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/rituaH/1538

View MORE
Open in Telegram


ርቱዓ ሃይማኖት Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Pinterest (PINS) Stock Sinks As Market Gains

Pinterest (PINS) closed at $71.75 in the latest trading session, marking a -0.18% move from the prior day. This change lagged the S&P 500's daily gain of 0.1%. Meanwhile, the Dow gained 0.9%, and the Nasdaq, a tech-heavy index, lost 0.59%. Heading into today, shares of the digital pinboard and shopping tool company had lost 17.41% over the past month, lagging the Computer and Technology sector's loss of 5.38% and the S&P 500's gain of 0.71% in that time. Investors will be hoping for strength from PINS as it approaches its next earnings release. The company is expected to report EPS of $0.07, up 170% from the prior-year quarter. Our most recent consensus estimate is calling for quarterly revenue of $467.87 million, up 72.05% from the year-ago period.

Spiking bond yields driving sharp losses in tech stocks

A spike in interest rates since the start of the year has accelerated a rotation out of high-growth technology stocks and into value stocks poised to benefit from a reopening of the economy. The Nasdaq has fallen more than 10% over the past month as the Dow has soared to record highs, with a spike in the 10-year US Treasury yield acting as the main catalyst. It recently surged to a cycle high of more than 1.60% after starting the year below 1%. But according to Jim Paulsen, the Leuthold Group's chief investment strategist, rising interest rates do not represent a long-term threat to the stock market. Paulsen expects the 10-year yield to cross 2% by the end of the year. A spike in interest rates and its impact on the stock market depends on the economic backdrop, according to Paulsen. Rising interest rates amid a strengthening economy "may prove no challenge at all for stocks," Paulsen said.

ርቱዓ ሃይማኖት from us


Telegram ርቱዓ ሃይማኖት
FROM USA